Job Description:-
ኃላፊነት :-
- የኮርፖሬሽኑን ሥራዎች በበላይነት ማቀድ ፣ ማደራጀት ፣ ማስተባበር፣ መምራት ፣ ማቆጣጠር ፣
- የኮርፖሬሽኑን ከፍተኛ የሥራ አመራር ቡድን በማስተባበር ኮርፖሬሽኑ የሚሰራባቸውን የፖሊሲ ኃሳቦች ማመንጨት ሲፈቀድ ዝርዝር መመሪያዎችን በማውጣት ማስፈጸም ፣
- በማቋቋሚያ ደንቡ በኮርፖሬሽኑ የተሰጡትን ተልዕኮዎች ማስፈጸም፣
- ለአዳዲስና ለሚስፋፋ የኮርፖሬሽኑ የማዕድን ነዳጅና ባዮፊውል ፐሮጀክቶች ማስፈጸሚያ የሚሆን ፋይናንስ ማፈላለግ ፣ ቅንጅቶችን መፍጠር ፣
- የኮርፖሬሽኑ ወሳኝና ድጋፍ ሰጪ ዘርፍ ተናበውና ተቀናጅተው እንዲሰሩ ማድረግ ፣
- ለአመራር ቦርድ የሚቀርቡ ሪፖርቶችን በወቅቱ እንዲቀርቡ ማድረግ ፣ ማስወሰን ፣ ማስፈፀም ፣
- በሁለትዮሽ ግንኙነቶች ኮርፖሬሽኑን በበላይነት መወከል ፣
- የውጭ ኦዲተሮችን መድቦ የኮርፖሬሽኑን ዋና መስሪያ ቤት ፣ ፋብሪካዎችና ፐሮጀክቶች ማስመርመር ፡፡
Job Requirements:
- ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ :- ፒ.ኤች.ዲ/ኤም.ኤስ ሲ/ኤም .ኤ/ቢ.ኤስ.ሲ/ቢኤ ጂኦሎጂ ፣ በሜካኒካል/ኬሚካል ምህንድስና ፣ በማይኒንግ /በማይ ሰርቬይ ኢንጂነሪንግ ፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬስን ፣ በማኔጅመንት ፣ በኢኮኖሚስትና ተመሳሳይ በተጨማሪም ማኔጅመንት ዲቮሎፐመንት ስልጠና የወሰደ
- የሥራ ልምድ :- እንደቅደም ተከተላቸው በሙያው 10፣ 12፣ 14፣ ከዚህ ውስጥ 6 ዓመት በከፍተኛ ኃላፊነት የሠራ /የሠራች
- ደመወዝ :- 21,590.00
- የቅጥር ሁኔታ :- በቋሚነት
- የሥራ ቦታው :- አዲስ አበባ
- ብዛት :- አንድ ነው
How To Apply:
አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ያላችሁን የሥራ ልምድና የትምህርት ማስረጃ የማይመለስ ፎቶ ኮፒ በሰው ሀብት ልማትና አመራር መምሪያ በመቅረብ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
አድራሻ ፣ የኢትዮጵያ ማዕድን ነዳጅና ባዮፊውል ኮርፖሬሽን 22 ማዛሪያ አውራሪስ ሆቴል በስተጀርባ ስልክ ቁጥር 0116-61-13-62 /0116-61-33-55
