Job Expired

company-logo

Personnel & General Officer

Minaye PLC

job-description-icon

Business

Human Resource Management

Addis Ababa

3 years - 4 years

1 Position

2024-06-26

to

2024-06-28

Required Skills
Required skills have not yet been specified for this position this job
Fields of study

Public Administration

TVET

Management

Full Time

Share

Job Description

ክፍሉን ሥራ ማቀድና ማደራጀት፣ ማስተባበር፣ መምራትና መቆጣጠር፣ የድርጅቱን የሰው ኃይል ቅጥር፣ ዕድገት፣ ዝውውር እንዲሁም ስንብት ፎርማሊቲን ማከናወን፣ በሠራተኞች ዘንድ የሥራ ዲሲፕሊን እንዲከበር ማድረግ፣ የመብራት፣ የውኃ፣ የስልክ፣ የትራንስፖርትና የጥበቃ፣ የጽዳትና የመላላክ የፎቶ ኮፒ አገልግሎት የተሟሉ መሆናቸውን መከታተልና መቆጣጠር፣ የድርጅቱን መኪናዎች ለስራ ማሰማራትናመቆጣጠር፣ የመኪኖቹን ደህንነት ማረጋገጥ፣ልዩ ልዩ የሥራ ልብሶች በወቅቱ ለሠራተኛው መድረሳቸውን ማረጋገጥ የጠቅላላ አገልግሎት ሥራዎች የሚቀላጠፉበትንና የሚሻሻሉበትን መንገድ በማጥናት ማቅረብና ሲፈቀድ ሥራ ላይ ማዋል።

የስራ ቦታ :-ቃሊቲ

ዝርዝር የሥራ ተግባር 

  • የዋና ክፍሉን ሥራ ያቅዳል፣ ያደራጃል፣ በሥሩ ያሉትን ሠራተኞች ይመራል፣ ያስተባብራል፣ ይቆጣጠራል፤

  • በድርጅቱ የአስተዳደር ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች መሠረት የድርጅቱን የሰው ሀይል ያስተዳድራል፣ ቀልጣፋ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲዘረጋ ያደርጋል፤

  • በተለያዩ ምክንያት ድርጅቱን በሚለቁ ሠራተኞች ምትክ ተገቢው የሰው ኃይል እንዲተካ ለሚመለከታቸው የዘርፍ ሃላፊዎች ያሳውቃል፣ለቅጥሩም ቅድመ ዝግጅት ያደርጋል፤

  • ለድርጅቱ ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውሉትን የውኃ፣ የመብራት፣ የስልክ፣ የነዳጅ፣ የትራንሰፖርት፣ እንዲሁም ኢንሹራንስ፣ ለመዝናኛ ክበብ አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎች መሟላታቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ ያልተሟሉ መገልገያዎችና ዕቃዎች ካሉ እንዲሟሉ ዝርዝር ሪፖርት ለቅርብ አለቃው ያቀርባል፣ አፈፃፀሙንም ይከታተላል፤

  • የጠቅላላ አገልግሎት ሥራ በተሻለ ቅልጥፍናና ጥራት ስለሚሰጥበት ሁኔታ ጥናት በማድረግ ለሃላፊው አቅርቦ ያስወስናል፣ ሲፈቀድም ሥራ ላይ መዋሉን ይቆጣጠራል፤ ለክፍሉ የሚያስፈልገውን በጀት በማዘጋጀት ያስፈቅዳል ተግባራዊነቱንም ይከታተላል ያረጋግጣል፤

  • የድርጅቱ የግቢ ጥበቃ አስተማማኝ መሆኑን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፤

  • ለድርጅቱ ሠራተኞች የሚያስፈልጉ የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች፣ መሣሪያዎችና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች በወቅቱ መሟላታቸውን ይከታተላል ይቆጣጠራል፤

  • በድርጅቱ ደንብና መመሪያ መሠረት ለሠራተኞች መስጠት የሚገባው የሥራ ላይ የአደጋ መከላከያ የሥራ ልብስና የመሳሰሉት በወቅቱ እንዲደርሳቸው ያደርጋል፡፡

  • በኢንሹራንስ ፖሊሲ መሠረት የድርጅቱ ንብረትና የድርጅቱ ሠራተኞች የመድን ዋስትና ማግኘታቸውን ይከታተላል፤ በየዘመኑ መታደሱን ያረጋግጣል፤

  • በንብረት ወይም በሰው ላይ አደጋ በደረሰ ጊዜ በተገቢው የመድን ዋስትና መሠረት የካሳ ጥያቄ /claim/ በማድረግ ተከታትሎ ያስፈጽማል፤

  • የተሽከርካሪዎች የሕይወት ታሪክ፣ የነዳጅና የቅባት ፍጆታ የጥገና ወጪን በተመለከተ አስፈላጊ መረጃዎች በሙሉ መሟላታቸውን ያረጋግጣል፤

  • ማንኛውም የድርጅቱ ንብረት ተገቢ ጥበቃና ጽዳት የተሟላ መሆኑን፣ የቢሮ መሣሪያዎች፣ ቋሚ ንብረቶች፣ ተሽከርካሪዎችና ሕንፃዎች አስፈላጊው ጥገናና ዕድሳት በሚያስፈልጋቸውና ከቅርብ አለቃው ሲፈቀድ በሚተላለፍለት መመሪያ መሠረት ጥገናዎቹ በወቅቱ እንዲከናወኑ በመከታተል ያስፈጽማል፤

  • የድርጅቱ ቢሮዎች ሕንፃ፣ ግቢና የመገልገያ መሣሪያዎች ወቅታዊ ጥገናና ዕድሳት እንዲደረግላቸው ይከታተላል፤

  • የእሳት አደጋ መከላከያዎች በየቦታው ተሟልተው እንዲቀመጡና በየአካባቢው ያሉ ሠራተኞችም በሙያው በቂ ስልጠና እንዲያገኙ ያደርጋል፤

  • ለጥበቃ፣ ለጽዳት ሠራተኞች፣ ለተላላኪዎችና ለሰርቪስ ሾፌሮች ወዘተ…….አስፈላጊውን የሥራ ፕሮግራም በማውጣት ይደለድላል አፈጻጸሙን ይቆጣጠራል፤

  • የስልክ፣ የመብራትና የውሃ መስመሮች አገልግሎት ሲያቋርጡ ከሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች ጋር በአስቸኳይ በመነጋገር አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ ያደርጋል፤

  • የፎቶ ኮፒና የህትመት አገልግሎቶች በተሟላ ሁኔታ መስጠታቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፤

  • የስልክ አጠቃቀም፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ፍጆታ በቁጠባ እንዲሆን ይከታተላል፣ ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን እየተከታተለ ያስፈጽማል፤

  • በአዲስ ወይም በነባር የሥራ መደቦች ላይ ሠራተኞች ለመመደብ አስፈላጊ ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ በቅርብ ኃላፊው በሚሰጠው መመሪያ መሠረት ለተወዳዳሪዎች ማስታወቂያ ያወጣል፣ ተወዳዳሪዎችንም ማስረጃዎቻቸውን አረጋግጦ ይመዘግባል፤

  • የሠራተኞች የሥራ አፈጻጸም ምዘና ሪፖርት በወቅቱ ተሞልቶ በሠራተኞች የግል ማኅደር ውስጥ እንዲካተትና እንዲቀመጥ ያደርጋል፤

  • የሠራተኛ ቅጥር ወይም ዕድገትና ዝውውር እንዲሁም ጡረታና ስንብት በሚፈጸምበት ጊዜ አዋጅንና ኅብረት ስምምነቱን ተከትሎ አስፈላጊውን ይፈጽማል፤

  • የድርጅቱ የሥራ ሰዓትና የሥራ ዲሲፕሊን እንዲከበር ከሚመለከታቸው የሥራ ቅንጅት ይፈጥራል፣ የሠራተኞች የዲሲፕሊን ሁኔታ እንዲሻሻልና የሥራ ተነሳሽነት እንዲጎለብት አስፈላጊውን ሥልጠና ይሰጣል፤

  • የድርጅቱን የሥራ እንቅስቃሴ በማይጎዳ መንገድ ሠራተኞች የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን በወቅቱ እንዲወስዱ ከቅርብ ኃላፊው ጋር በመመካከር ፕሮግራም ያዘጋጃል፣ አፈጻጸሙን ይከታተላል፤

  • የሠራተኞች ደመወዝና የትራንስፖርት አበል በወቅቱ እንዲከፈል ከሰዓት ቁጥጥር ሰራተኛ የሚቀርብለትን መረጃ መሠረት በማድረግ በማጣራትና በማረጋገጥ ዝርዝሩን በወቅቱ ለሂሳብ የሥራ ዘርፍ እንዲተላለፍ ያደርጋል፤

  • የድርጅቱ ሠራተኞች የሚያቀርቡትን የሕክምና የተለያዩ የፈቃድ ማስረጃዎች ከአዋጁና ከድርጅቱ የአስተዳደር መመሪያ ጋር አመሳክሮና አረጋግጦ ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ያስተላልፋል፤

  • በሠራተኞች የግል ማኅደሮች ውስጥ መያዝ የሚገባው መረጃዎችና ሰነዶች ተሟልተውና ሚስጥራቸው ተጠብቆ መያዛቸውን ያረጋግጣል፤

  • በሥሩ ለሚገኙ ሠራተኞች ሚዛናዊ የሆነ የሥራ ሥምሪት ይሰጣል የሥራ አፈጻጸማቸውን ይገመግማል ሪፖርት ያደርጋል፤

  • በተጨማሪም ሌሎ ከቅርብ ኃላፊው የሚሰጠውን ተመሳሳይ ሥራዎችን ያከናውናል፤

የስራ መስፈርቶች

  • ከታወቀ ዩኒቨርስቲ/ ኮሌጅ ዲግሪ ወይም በቀድሞው የትምህርት ፖሊሲ 12+4 ወይም በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ 10+3 በሥራ አመራር፣ ሕዝብ አስተዳደር ወይም በተመሳሳይ የትምህርት መስክ የተመረቀ/ች

የስራ ልምድ

  • 3 ዓመት የሥራ ልምድ ያለው/ላት

የማመልከቻ መመርያ

  • አመልካቾች የትምህርት፣ የሥራ ልምድ ደብዳቤ የማይመለስ ኮፒ ይዛችሁ በድርጅቱ ኢ-ሜይል: hrminaye@gmail.com ወይም ቃሊቲ ገብርኤል ኢንዱስተሪያል መንደር አካባቢ ዴሉክስ ፈርኒቸር ፋብሪካ በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን። ለበለጠ መረጃ ስልክ 0114717381

Fields Of Study

Public Administration

TVET

Management

Related Jobs

5 days left

Yoha International Pharmaceuticals PLC

HR & Admin Officer

Human Resource Officer

time-icon

Full Time

5 yrs

1 Position


Bachelor's Degree in Human Resource Management, Business Administration or in a related field of study with relevant work experience Duties & Responsibilties: - Assist in the recruitment process: posting job ads, screening resumes, scheduling interviews. - Prepare employment contracts, onboarding documentation, and conduct employee orientation. - Maintain and update employee records (digital and physical).. - Oversee general office operations including maintenance, supplies, and equipment. - Manage office filing systems, correspondence, and documentation. - Coordinate meetings, events, and travel arrangements.

Addis Ababa

19 days left

ANDEMAMMA Manufacturing PLC

HR and Administration Officer

Human Resource Officer

time-icon

Full Time

2 - 6 yrs

1 Position


Bachelor's Degree in Business Administration, HRM or in a related field of study with relevant work experience Duties & Responsiblites: - Manage the recruitment and onboarding process for new hires. - Maintain and update employee records and HR databases. - Prepare employment contracts and process HR documentation. - Support employee performance evaluations and training programs. - Address employee inquiries and resolve workplace issues professionally. Required Skills: - High level of integrity and confidentiality. - Proactive, adaptable, and solution-oriented. - Passionate about fostering a positive organizational culture. - Strong business acumen with a strategic mindset. - Collaborative and approachable, focusing on team development and organizational goals.

Addis Ababa

21 days left

SHANGTEX GARMENT MANUFACTURING ETHIOPIA PLC

HR Manager

Human Resource Management Specialist

time-icon

Full Time

2 - 5 yrs

1 Position


PhD, Master's or Bachelor's Degree in Human Resource Management or in a related field of study with relevant work experience Duties & Responsibilities: - Supervise and implement the company's existing HR management system, ensure that daily work is executed in an orderly manner and implemented in accordance with regulations, and maintain the company's authority. - Responsible for the recruitment of all local employees, complete the recruitment tasks within the specified time, and be responsible for the results. - Responsible for training local employees and tracking the results. The training includes but is not limited to company culture, factory disciplines, relevant laws and regulations, and customer compliance requirements. - Assist other departments to handle employee complaints and improve employee relations to ensure that daily work and production are not affected and there are no major strikes.

Addis Ababa

about 7 hours left

Ethiopian Press Agency

Human Resources Management Specialist III

Human Resource Management Specialist

time-icon

Full Time

0 yrs

1 Position


PhD, Master's or Bachelor's Degree in Management, Human Resource Management, Public Administration or in a related field of study with relevant work expereince Experience: 4 years for Bachelor's, 2 years for Master's and 0 years for PhD Duties & Responsibilities: - Lead the design and implementation of HR strategies, policies, and procedures aligned with organizational goals. - Oversee and guide recruitment processes, onboarding programs, and workforce planning initiatives. - Manage complex employee relations issues and ensure compliance with labor laws and internal regulations. - Coordinate performance management processes, including training, coaching, and evaluation systems. - Analyze HR metrics and workforce data to support strategic decision-making.

Addis Ababa

about 7 hours left

Medical Teams International

HR Intern

Internship

time-icon

Full Time

0 yrs

1 Position


BA Degree in Management, Human Resource Management, Public Administration or in a related field of study Duties and Responsibilities: - Maintain personnel and confidential files for active and terminated employees. - Fill out employment and other HR forms. - Facilitate staff medical insurance.

Addis Ababa

about 7 hours left

RC Construction

Human Resource Management

Human Resource Management Specialist

time-icon

Full Time

8 yrs

1 Position


Bachelor's Degree in Human Resource Management, or in a related field of study, with relevant work experience

Addis Ababa